ተቋማዊ የባህል ግንባታ ለአንድ ተቋም ራዕይ ተል...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ተቋማዊ የባህል ግንባታ ለአንድ ተቋም ራዕይ ተልዕኮ እና ግቦች መሳካት ሚናው የጎላ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ይህ የተገለጸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ የስነ-ምግባርና በፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት  ለፍትህ ቢሮ ሰራተኞች ተቋማዊ ባህል ግንባታ  እና በስራ ስነ-ምግባር ዙሪያ ስልጠና በሰጠበት ወቅት ነው፡፡ተቋማዊ የባህል ግንባታ ለአንድ ተቋም ራዕይ ተልዕኮ እና ግቦች መሳካት ሚናው የጎላ መሆኑ የገለጹት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሲሳይ በፍቃዱ ናቸው፡፡  በመድረኩ ተቋማዊ ባህል ግንባታ  እና በስራ ስነ-ምግባር ጠቀሜታ ተያያዥ ሀሳቦች ላይ ማለትም  ስለ ስነ-ምግባር ምንነት፣ ስለ ስነ-ምግባር ምንጮች/ መሰረቶች፣ ስለ ስራና ሙያ ምንነት፣ ስለ ስራና ሙያ ስነ-ምግባርና ፋይዳው/ጠቀሜታው እንዲሁም ሌሎችም ተዛማጅ ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ ሰፊና አሳታፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በመጨረሻም የስልጠናው አጠቃላይ ሂደት ጥሩ እንደነበር በማመስገን  የገለጹት ተሳታፊዎቹ  ለተነሱት ሃሳብና አስተያየቶች ፍትህ ቢሮ የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሲሳይ በፍቃዱ ናቸው፡፡

ጥቅምት 21/2018

ፍትህ ቢሮ  


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.